ግንቦት 28 የበዓለ እረፍት መታሰቢያ | ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሐይማኖት ሶስተኛው ፓትርያርክ


የወንጌል ገበሬ የድሆች አባት ገንዘብ በእጃቸው የማይነኩ ሙሉ ደሞዛቸውን ሰንበት ትምህርት ቤት ማጠናከሪያ ለሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ያዋሉ ከድንችና በሶ በቀር ምናምኒት በአፋቸው የማይዞር ጸዋሚ ተሐራሚ የምድረ ወላይታ ሐዋሪያ አባ መልአኩ 400ሺ ህዝብ አስተምረው ያጠመቁ 65 ቤተክርስቲያን 24 ትምህርት ቤት ያሰሩ ይህን ሁሉ ሲሰሩ ከስብከተ ወንጌል ፈቃድ ውጪ አለ ደሞዝ አበል ሳይጠይቁ ሞንታርቦ እንደዘመነኞች ሳይጎትቱ በባዶ እግራቸው አልጫውን በወንጌል ያጣፈጡ ሐዋሪያ ከፍ ላለው ክብርም በቅተው የአራት ኪሎ ውሐ ያልቀየራቸው በዘር ከረጢት ያልተቁዋ ጠሩ አብረሐማዊ ያን የደም ዘመን ጸሎታቸው ሐመር ሆኖ ህዝብን ያሻገረ በጊዜ ሞታቸው ስጋቸው አልቆ 25 ኪሎ የመዘኑ መናኝ የቅዱሳን ወዳጅ የመንጋው ታማኝ እረኛ ቤተክርስቲያን ያገለገሉ እንጂ ያልተገለገሉባት ሲሳይዋን ያላሳሱ አባታችን ግንቦት 28 ቀን 19 80 ዓ/ም በሞተ ስጋ ያንቀላፉበት ቀን ናት በረከታቸው ትደርብን ንዕድ ክብርት ስሙር ጸሎታቸው ማይ ሆና በላያችን ትንጠብ እንዲህ ያሉትን ደጋግ ያምጣልን። አሜን።
Share on Google Plus

ስለ የተለጠፈበት ቀን

    Blogger Comment
    Facebook Comment