ጠቢባን የሆኑ አባቶቻችን የዘመን ስሌትን በሚገባ ተንትነው ዘመናዊቷ አለም ከምትጠቀምበት አቆጣጠር ረቀቅ ባለ መልኩ እስከ ሳድሲት ማለትም 0.00000185 ሰከንድ ድረስ አስለተዋል።
መሬት በፀሐይ ላይ የምታደርገው ኡደትን ተረድተው የጊዜ መለኪያ እና መቁጠሪያ አስቀመጠውልናል ....
በቀን 1 ኬክሮስ በ30 ቀን 30 ኬክሮስ ይሆናል።
በ2 ወር 60 ኬክሮስ ይሆናል። 60 ኬክሮስ ደግሞ 1 እለት ስለሆነ። በ2 ወር 1 እለት በ12 ወር 6 እለት ታበራለች ማለት ነው። በ12 ወር ወይም በአንድ ዓመት 5 ቀንና 15 ኬክሮስ ከ1 ሣልሲት ይሆናል።...... የቀረችው 52 ካልዒትን ልቀይረው.... 52 ካልዒት×30 ቀን×12 ወር=18720 ካልዒት በዓመት ይገኛል።
ይህ ማለት የ52 ካልዒትየ 30+(1) ሳልሲት ጠቅላላ ስንደምረው ... 312+3=315 ኬክሮስ ይሆናል።
የተረፈችው 15 ኬክሮስ ለ4 አመታት ስትጠራቀም... በ4 ዓመት 4×15=60 ኬክሮስ ወይም አንድ እለት ይሆናል። በአራት ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 6 የምትሆን በዚህ ምክንያት ነው።.....
ከላይ የ30ዋን ሳልሲት ሰርቸ አንዷን አላሰላሆትም....አንዷ ሣልሲት በ600 ዓመት 1 ቀን ትሆናለች።ይኽውም 1 ሣልሲት×30 ቀን×12 ወር×600 ዓመት 216000 ሣልሲት ይገኛል ይህንን ወደ ኬክሮስ ስንቀይረው 60 ኬክሮስ ይሆናል።
60 ኬክሮስ ደግሞ አንድ ቀን ወይም እለት ነው። ስለዚህም በ600 ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 7 ትሆናለች ማለት ነው።...ወይም በቀላል መንገድ ላሳያችሁ...
አንድ ቀን =365 እለት ከ 15 ኬክሮስ ከ 6 ካልዒት / ወይም 365 ቀን ከ 6 ስዓት ከ 2 ደቂቃ ከ 24 ሰከንድ ነው...36o ቀን + 5 ቀን ጳጉሜ .. ይሆንና 6 ስአት ከ 2 ደቂቃ ከ 24 ሰከንድ ትተርፍለች... የተሰባሰበችው 6 ስአት በ አራተኛው አመት 24 ስአት ወይም አንድ ቀን ስትሆን ጳጉሜ 6 ትሆናለች። ትራፊ 2ደቂቃ ከ 24 ሰከንዷ ትሰበሰባለች ይህ ማለት በ 600 አመት 24 ስአት ወይም አንድ ቀን ትሞላለች።
ስለዝህ ሊቃውንቱ በተገለጠላቸው መጠን 11 ጥንተ አበቅቴ ይባላል።
#መጥቅዕ ማለት ትረጉሙ ደወል ሲሆን አጽዋማትን እና በዓላትን የሚያስገኝ ነው ከዚህ ላይ ተንተረሰን በዚህ ቀን ይህ ጾም በዚህ ዕለት ይህ በዓል በእንዲህ ቀን ለማለት ያስችላል...።
መጥቅዕ እና አበቅቴ ተደምረው 30 መሆን ስላለባቸው መጥቅዕ 30-11=19 ይሆናል።
#ስለዚህ በመጀመሪያው ዓመት 11 አበቅቴ ከሆነ በሁለተኛው አመት 22 ይሆናል በሦስተኛው 33 ይሆናል። ከ30 በላይ ሲሆን በ30 አካፍለን ቀሪውን እየያዝን አበቅቴን እናወጣለን ስለዚህ 3 ይሆናል። ከዚያ በአራተኛው 3+ 11=14 እያለ ይሄዳል። አበቅቴና መጥቅእ ሁለቱ ተደምረው 30 ስለሚሆኑ አንዱ ከተገኘ ሌላኛውን ከ30 በመቀነስ እናገኘዋለን።
አለም ከተፈጠረች ጠቅላላ ዕድሜ 5500+2016=7514 አመት....ስለዚህ በሚቀጥለው ዓመት ዘመኑ ዘመነ ማን ነው የሚለውን ለማወቅ ስንፈልግ ዓመተ ዓለሙን ለ4 አካፍለን ቀሪው 1 ከሆነ ዘመነ ማቴዎስ ፤ቀሪው 2 ከሆነ ዘመነ ማርቆስ ፤ቀሪው 3 ከሆነ ዘመነ ሉቃስ ያለ ቀሪ ከተካፈለ ዘመነ ዮሐንስ ነው።
የዓመቱ መስከረም 1 ቀን መቼ መቼ ትውላለች?
ታህሣሥ 19 ሰኞ ከዋለ ሐምሌ 19ም ሰኞ ይውላል ማለት ነው።.. አጽዋማትና በአላትን ዕለት ለማውጣት የምንጠቀምበት መባጃ ሐመር ይባላል ይህንን ለመቀመር የምናገኘው መጥቅዕ+መጥቅዕ የዋለበት የእለት ተውሳክ አድርገን ማገኝነት ይቻላል!!!
Blogger Comment
Facebook Comment