💭 ሊቀ ጳጳስ ቪጋኖ ስለ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስኮ፡ “ለሠሯቸው ወንጀሎች ተጠያቂ ይሆናሉ”


✍ ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ | ኢትዮጵያ አውታር

ሊቀ ጳጳስ ካርሎ ማሪያ ቪጋኖ በግዛት ዘመናቸው በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስኮ ላይ በተደጋጋሚ ተቺ ነበሩ። ቪጋኖ ጳጳስ ፍራንሲስኮ ለክፍት ድንበሮች እና ለሶሻሊዝም የሚያደርጉትን ድጋፍ በመቃወም በተደጋጋሚ ተናግረዋል።

ለቪጋኖ የማያቋርጥ ውግዘት ምላሽ፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስኮ እ.አ.አ በሐምሌ 2024 ቪጋኖን በልዩነት እንዲገለሉ አድርገዋቸው ነበር።

ሊቀ ጳጳስ ቪጋኖ በቤተክርስቲያኗ ላይ የሚደርሰውን ጥፋት፣ የኮቪድ/ COVID ዓለም አቀፍ የግለሰብ መብቶችን የሚጨፈጭፍ እና የተሰረቁ ምርጫዎችን በመቃወም ብዙ ነቀፋ የተሞላበትን ድምጻቸውን በተደጋጋሚ አሰምተዋል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳ ፍራንሲስኮ በቤተክርስቲያኒቱ ላይ ለፈጸሙት አጥፊ ተግባር እና እንደ የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ላሉ የክርስቶስ ተቃዋሚ ድርጅቶች ድጋፍን በመስጠታቸው ነው ቪጋኖ የወቀሷቸው። በዚህም ምኪንያ ቪጋኖ ከካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን እንዲወገዱ ተደርገዋል።

እ.ኤ.አ. በ 2018 ጣልያናዊው ጋዜጠኛ፣ ፀሐፊና ፖለቲከኛ ዩጂንዮ ስካልፋሪ ጳጳስ ፍራንሲስኮ ከሞት በኋላ ስላለው ሕይወት ስላላቸው ራዕይ ጠይቋቸው ጳጳሱ ያካፈሉት ቃል እንዲህ እንዳሉት ዘግቧል፡-

"ኃጢአተኛ ነፍሳት አይቀጡም፤ ንስሐ የገቡ የእግዚአብሔርን ይቅርታ ያገኛሉ እና እርሱን ከሚያስቡት ነፍሳት ጋር ይቀላቀላሉ፣ ነገር ግን ንስሃ የማይገቡ እና ስለዚህ ይቅር የማይባሉት ይጠፋሉ፣ ሲኦል የለም፣ ኃጢአተኛ ነፍሳት በቀላሉ ይጠፋሉ።"

ይህንም ኢ-ክርስቲያናዊ የሆነ የርዕሰ ጳጳሳት ፍራንሲስኮ ራዕይ አሁን ከሞቱ በኋላ ሊቀ ጳጳስ ቪጋኖ እንዲህ በማለት ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፤

እነዚህ የመናፍቃን ቁጣዎች ከካቶሊክ እምነት ጋር በቀጥታ ይቃረናሉ፣ ይህም ለሁሉም ሰው የተለየ ፍርድ እንዳለ ያስተምረናል፣ ከዚህም ፍርድ ጳጳስ ፍራንሲስኮ በፍጹም ሊያመልጡ አይችሉም። ስለዚህም ነፍሳቸው አልጠፋችም፣ አልተፈታችምም፣ ለሠሩት ወንጀል ተጠያቂ ይሆናሉ፣ በመጀመሪያ የጴጥሮስን ዙፋን በመንጠቅ የካቶሊክን ቤተክርስትያን ለማጥፋት እና ብዙ ነፍሳትን ለማፍሰስ ወንጀል ሠርተዋል።"

Share on Google Plus

ስለ የተለጠፈበት ቀን

    Blogger Comment
    Facebook Comment