የትንሣኤ ዕሑድ፣ የኢየሱስን ከተፈጥሮ በላይ የሆነ ትንሣኤን አከበርን፤ ይህም ከክርስትና ሃይማኖታችን ዋና ዋና ነገሮች አንዱ ነው። በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ለሚታመኑ ሰዎች " ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ" ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ጽፏል። (፩ ቈረንቶስ ፲፭)
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በ፹፰/88 ዓመታቸው በፋሲካ ሰኞ አረፉ/ሞቱ።
ስምንት ቁጥር በጣም አስፈላጊ ከመሆኑ የተነሳ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ፸፫/73 ጊዜ ተጠቅሷል። የትንሣኤ እና የመታደስ ምልክት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ የቁጥር ቀመር ጥናት ስምንት ማለት አዲስ ጅምር ማለት ነው። እሱም “አዲስ ሥርዓትን ወይም ፍጥረትን እንዲሁም የሰው ልጅ ከሙታን ተነሥቶ ወደ ዘላለማዊ ሕይወት ሲመለስ የሚያደርገውን እውነተኛ ‘ዳግመኛ መወለድ’ ያመለክታል። የመጀመሪያው ታሪካዊ ማጣቀሻ ለኖህ እና ለቤተሰቡ "ስምንት ሰዎች በውኃ ውስጥ በደኅና እንደ መጡ" (፩ ጴጥሮስ ፫፥፳)። እነዚያ ስምንቱ ሰዎች ጎርፉ ካረፈ በኋላ እውነተኛ አዲስ ጅምር አግኝተዋል። ሌላው በዘፍጥረት ፲፯፥፲፪ እያንዳንዱ ሕፃን በስምንተኛው ቀን እንደሚገረዝ ከአብርሐም ጋር የገባው የቃል ኪዳን ምልክት እንዲሆን በእግዚአብሔር የተቋቋመ ነው። ከአብርሐም ጋር የተደረገው ይህ ቃል ኪዳን ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን አዲስ ግንኙነት ያመለክታል።
Blogger Comment
Facebook Comment