ይህ ክብረ ነገሥት መጽሐፍ በመኖሩ የኢትዮጵያውያን ማንነት እና ታሪክ ምን ያህል ተቀየረ? ... መጽሐፉስ ባይኖር ኖሮ የኢትዮጵያውያን ብሎም የዓለም ታሪክ ምን ያህል ይቀየር ነበር ፣ አንዳንድ ሃገራት ሙሉ ለሙሉ ከዓለም ካርታ ላይ ላይኖሩ ይችሉ ነበር... ስለነዚህ ጉዳዮች ቀጥለን እናያለን።
በክብረ ነገሥት መጽሐፍ ላይ የሚነሱት ዋና ዋን ነጥቦች፦
- የሰሎሞን ሥርወ መንግሥት መሠረት
- የንግሥተ ሳባ እና የንጉሥ ሰሎሞን ጉዞ
- የቃል ኪዳኑ ታቦት ወደ ኢትዮጵያ መምጣት
- የኢትዮጵያውያን ከጣዖት አምልኮ ወደ ክርስትና መሸጋገር ናቸው።
ከነዚ ነጥቦች ጀርባ ግን አንድ ትልቅ ጉዳይ በታሪክ መጽሐፉ መልክት ውስጥ አብሮ ይተላለፋል... ይህንን ጉዳን ከማንሳታችን በፊት ግን መጽሐፉ በመኖሩ እና ባይኖር ብለን የዓለም ታሪክ ምን ያህል ይለወጥ ነበር የሚለው እንመልከት።
አብርሃም እግዚአብሔርን በመፈለጉ ትእዛዛቱንም ሁሉ በመፈጸሙ እግዚአብሔር ለአብርሃም ቀጥሎም ለይስሃቅ እና ለያቆብ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል ይህም ታላቅ ህዝብ እንደሚያደርጋቸው፣ ርስት የምትሆናቸውን ሃገር እንደሚሰጣቸው፣ አህዛብም በነሱ በኩል እንደሚባረኩ ቃል ገብቶላቸዋል... እግዚአብሔርም በቃል ኪዳኑ መሠረት ከያቆብ አስራሁለቱን ነገደ እስራኤልን እንዳወጣ እና እንዳበዛቸው ታላቅ ህዝብም እንዳደረጋቸው፣ ርስት የምትሆናቸውን የከነአን ምድርም እንደሰጣቸው፣ እሰራኤልም ደግሞ የእግዚአብሔር ህዝብ በመሆናቸው ከሌላው አህዛብ የሚለያቸውን ኦሪትን ህግጋት እና ስርዓት እንደሰጣቸው በመጽሕፍ ቅዱስ ላይ ያለ ታሪክ ነው።
የኦሪት ህግጋት የተሰጡት ለእስራኤላውያን ብቻ እንደሆነ እስራኤላውያን እነዚህን የኦሪት ህግጋት እና ስርዓቶች ለሌላው ህዝብ ወይም አህዛብ የመስበክ፣ አህዛብም የኦሪትን ሕግጋት የመጠበቅ ግዴታ እንደሌለባቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልጽ ተቀመጦ እናየዋለን።
ለምሳሌም እስራኤላውያን ሃገር መስርተው፣ ንጉሥ አግሠው፣ ኃያል ሆነው በዙራያቸው ያሉ አህዛብን በሚያስገብሩበት ጊዜ ወደ አህዛብ ሄደው የኛን የኦሪትን ህግ እና ስርዓት ተከተሉ ብለው ተጽእኖ የፈጠሩበት በዚህን መልኩ ሰዎችን የቀየሩበት እንድም አጋጣሚ የለም፣ በሌላ መልኩ ደግሞ እስራኤላውያን አቅም አጥተው ከሃገራቸው ተሰደው ወደ በተለያየ ሃገራት በኖሩባቸው ጊዜያት ለምሳሌ ወደ ግብጽ ፣ ወደ ባቢሎን ፣ ወደ ሮም ግዛቶች ሁሉ ሲሰደዱ የራሳቸውን የኦሪትን ህግ እና ስርዓቶችን ጠብቀው ከአህዛብ ጋር ሳይጋቡ እራሳቸውን ለይተው የመኖር ልምድ እንዳላቸው እንጂ ኦሪትን ለሌላው ህዝብ እንስበክ ከአህዛብ ጋር ተዋልደን ዘራችንን እናብዛ በፍጹም አይሉም አያደርጉም ነበር።
በአጠቃላይ የኦሪትን ህግጋት የመጠበት ግዴታ ያለባቸው የአብርሃም ዘር የሆኑት ህዝብ ብቻ ናቸው ማለት ነው፣ የኦሪት ስርዓት ካለ እስራኤላውያን እዛ እሉ ማለት ነው።
ታዲያ ይህንን የእስራኤላውያን ታሪክ እውነታ ከተረዳን ቡሃላ ወደ ኢትዮጵያ ስንመለከት ፣ የኦሪት ስርዓት በኢትዮጵያን ህዝቦች ዘንድ ከጥግ እስከ ጥግ ክላይ እንከታች ድረስ ስትፈጸም እናያለን ፣ ከታቦተ ጽዮን ጀምሮ ፣ የኦሪት መስዋእት ማቅረቢያዎች እና ምኩራባት በሃገሪቱ የተለያየ ቦታዎች መኖር፣ የኦሪት መጻህፍት መኖር፣ የሰንበት አከባበር ፣ የሚበሉ እና የማይበሉ እንስሳት መለየት ፣ ግርዛት ፣ የበዓላት አከባበር፣ የቤተ ክህነት መገልገያ እቃዎች እና ስርዓት፣ የዜማ መሳሪያዎች (በገና ማሲንቆ)፣ ሌሎችም ብዙ የኦሪት ህጎች እና ስርዓት በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሲተገበሩ በምናይበት ጊዜ ሁለት አይነት ድምዳሜ ላይ ያደርሰናል።
አንደኛው ኢትዮጵያውያን የኦሪትን ስርዓት የሚፈጽሙት ወደ ሃገራቸው ከሄዱት በጣም ጥቂት እራኤላውያን ተምረውት ነው ...
ሁለተኛው ደግሞ በቃ ይህንን ሁሉ የኦሪት ስርዓት ያላቸው ኢትዮጵያውያን እራሳቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያሉት እስራኤላውያን ናቸው ማለት ነው።
ሁለተኛው መደምደሚያ አሁን ላሉት እስራኤልነን ብለው ላሉት አይሁዳውያን እንደ እሬት እጅግ በጣም የሚመር በፍጹም በፍጹም መስማት የማይፈልጉት እውነታ ነው፣ ይሄ እውነት የነሱን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል ፣ የዘር ግንዳቸው ሃሰተኛነት የሚያረጋግጥ አሁን ያለቸው እስራኤል የምትባለው ሃገር ላትኖር የምችልበት አጋጣሚ ሁሉ የሚፈጥር ነው ፣ ምክንያቱም እውነተኞቹ እስራኤሎች ያሉት ኢትዮጵያ ከሆነ ሌላ እስራኤል የምትባል ሃገር እና ህዝብ አያስፈልግም ማለት ነው፣ በኦሪትም ላይ ወንጌል እንደተጨመረ የሚጠበቀው መሲህም እንደመጣ፣ መሲሁን ያልተቀበሉት የሰቀሉት እስራኤላውያን እንዳሉም፣ ክርስቶስን አምላክነቱን ጌትነቱ የተቀበሉ እስራኤላውያን እንዳሉ እነዚህም በኢትዮጵያ ያሉት ክርስቲያኖች እነደሆኑ በነቢያት የተነገረው ትንቢት ሁሉ እንደተፈጸመ ፣ የአሁኖቹን አይሁዳውያን ክህደታቸውን እና አታላይነታቸውን ስለሚያጋልጥ ኢትዮጵያውያን እውነተኛ ማንነታቸውን እንዲያውቁ የዓለምም ህዝብ እንዲያውቅ አይፈልጉም ...
ከአሁኖቹ አይሁዳውያን ተጨማሪም የአውሮፓውያኑ እና የምዕራባውያኑ የካቶሊኩም የፕሮቴስታንቱም የእስላሞችም መሠረት ይናጋል... ምክንያቱም እውነተኞቹ የመጽሐፍ ቅዱሶቹ እስራኤላውያን የተባሉት ኢትዮጵያውያን ከሆኑ የድሮዎቹ የእስራኤል ነገሥታት እነ ዳዊት ሰሞሎን፣ ነብያትም፣ ሐዋርያትም እመቤታችንም ጌታችንንም ሁሉ ፈረጆች ሳይሆኑ የአሁኖቹን የኢትዮጵያውያን መልክ ነበር ያላቸው አለባበሳቸውም፣ አኗኗራቸውም፣ ባህላቸውም የአሁኑን የኢትዮጵያውያን ባህል ነበር ማለት ነው። ይሄ ደግሞ ለአውሮፓውያን ለካቶሊክ እና ፕሮቴስታንቱ ዓለም የሞት ሞት ነው...
ስለዚህ እነዚህ ሁለ ኃይላት የኅልውናቸው መሠረት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ የኢትዮጵያን እውነታ እና ማንነት ለመቅበር ያላደረጉት ጥረት የለም ከነዛም መካከል በክብረ ነገሥት መጽሐፍ ውስጥ ያሉት ታሪኮች ዋናኞቹ ናቸው።
Blogger Comment
Facebook Comment