ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስኮ ሞት ጋር፣ የ፲፪/12ኛው ክፍለ ዘመን የአየርላንድ ሊቀ ጳጳስ የነበሩት የቅዱስ ማላቺይ አስደንጋጭ 'የጳጳሳት ትንቢት' ተፈፀመን?

✍ ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ | ኢትዮጵያ አውታር

ከቫቲካን የወጣ የ፱፻/900 አመት የትንቢት መፅሃፍ እንደሚለው 'የፍርድ ቀንበቅርቡ ሊመጣን ይችላል እና ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ የመጨረሻው የቤተክርስቲያኑ መሪ ሊሆኑ ይችላሉ።

የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሞት የ፱፻/900ዓመት ዕድሜ ለው “የጳጳሳት ትንቢት” (“Prophetia Sancti Malachiae Archiepiscopi, de Summis Pontificibus” ወይም “የቅዱስ-ሊቀ ጳጳስ ማላቺይ ስለ ሊቀ ጳጳሳት ትንቢት ፣)” በመባል ሚታወቀው መጽሐፍ እንደገና በሰዎች ላይ ፍላጎት አሳድሯል።

ቅዱሳት መጻሕፍቶቻችሁን በደንብ መፈተሽ ለምትፈልጉ፣ የፍርድ ቀን ፤ “የመጨረሻው ፍርድ” ወይም “የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት” በመባልም የሚታወቀው ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሰው ልጆች ላይ ለመፍረድ እና ምድርን እና ሰማይን ለማጥፋት ወደ ምድር የሚመለስበት ቀን ነው።

በዋናነት ማን እንደሚድን እና ማን እንደሚኮነን የምናውቅበት ቀን ነው።

ለአይራላንዳዊው ጳጳስ ቅዱስ ማላቺይ በተሰጠው የ፲፪/12ኛው ክፍለ ዘመን መጽሐፍ መሠረት፣ ይህ "የመጨረሻው ፍርድ..አ በ2027 ይካሄዳል።

Share on Google Plus

ስለ የተለጠፈበት ቀን

    Blogger Comment
    Facebook Comment