ገዳም ሚካኤል እምባ ደብረሲና/ አፅቢ ወምበርታ ትግራይ





✍ ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ 

የላሊበላ ዓብያተክርስቲያናት እናት የሆነው ጥንታዊው ገዳም ሚካኤል እምባ ደብረሲና ድንቅ ነው፤ ሀገራችንን አናውቃትም እኮ!

በአራተኛው መቶ ክፍለዘመን በ፫፻፴፰/ 338 ዓ.ም ላይ ቅዳሴ የተጀመረበት ታሪካዊ ገዳም ነው።

ገዳም ሚካኤል እምባ በምስራቅ ትግራይ ወረዳ አፅቢ ወምበርታ ሚካኤል እምባ ቀበሌ የሚገኝ ታሪካዊ ግዙፍ ውቅር ቤተክርስቲያን ገዳም ነው።

ከኣፅቢ ከተማ በ ፲፮/16 ኪሎሜትር አቅራቢያ የሚገኘው ይህ ታሪካዊ ገዳም የተሠራበት ዕለት በትክክል ባይታወቅም፤ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በ፫፻፴፰/338 ዓ.ም ላይ ቅዳሴ የተጀመረበት ገዳም ነው።

  • ❖ በ፫፻፴፰/338 ዓ.ም ላይ ቅዳሴ ተጀመረበት
  • ❖ በዘመነ ነገሥታት አብርሃ ወአፅብሃ እንደተሠራ ይነገራል
  • ❖ ፲፪/12 ጥልቅ ከአለት ተፈልፍለው የተሰሩ የውሃ ጎዳጉዶች አሉ ፣ ሰባቱ ሰውን እንዳይጎዳ ተብሎ ተደፍነዋል ፡ ፭/5የውሃ ጠበሎች አሉ
  • ❖ ፵፬/ 44 ምሶሶዎች ኣሉት

❖❖❖ የቅዱስ ሚካኤል በረከት በያልንበት ይድረሰን! እንደ እነ አብርሃ ወአፅብሃ ለእግዚአብሔር አምላክ የሚገዙና የሚታዘዙ ፍትሃዊ መሪዎችን ይስጠን! አሜን! አሜን! አሜን! ❖❖❖

✞✞✞[መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፲፮፥፲፪]✞✞✞

“ግፍን መሥራት በንጉሥ ዘንድ ጸያፍ ነገር ነው፥ ዙፋን በጽድቅ ይጸናልና።”

✞✞✞[መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፥፰]✞✞✞

“በፍርድ ወንበር የተቀመጠ ንጉሥ ክፉውን ሁሉ በዓይኖቹ ይበትናል።”

✞✞✞[መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ ምዕራፍ ፰፥፲፭]✞✞✞

“ዳዊትም በእስራኤል ሁሉ ላይ ነገሠ፤ ዳዊትም ለሕዝቡ ሁሉ ፍርድንና ጽድቅን አደረገላቸው።”


Share on Google Plus

ስለ የተለጠፈበት ቀን

    Blogger Comment
    Facebook Comment