ኢትዮጵያ ኢለን መስክ እና ጀፍሪ ኤፕስተይን

✍ ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ 

'ሞቷል' በተባለለትና የግራኝ አብዮት አህመድ 'አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ' ሞግዚት በሆነው በሕፃናት ደፋሪው በጄፍሪ ኤፕሽታይን ተጎጂ ለነበሩት ግለሰቦች ዶቼ ባንክ / የጀርመን ባንክ ፸፭/ 75 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ለመክፈል ወስኗል።

ግራኝ አሕመድ፣ ደመቀ ሐሰን፣ ጃዋር መሐመድ ወዘተ አውሬዎችና የሰዶም ዜጎች ናቸው። ሞቷል የተባለው ቅሌታሙ አሜሪካዊ ሕፃናት ደፋሪ ጄፍሪ ኤፕሽታይን አዲስ አበባ የሚገኘውንና ግራኝ ፈጥኖ ሁሉንም እንግዶቹን የሚያስጎበኘውን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ቆርቁሮታል። ይህን ገና ከጅምሩ ለማሳወቅ ሞክሪያለሁ። “የመንፈስ ማንነትና ምንነት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ለአዕምሮ መቆጣጠሪያ መሣሪያዎች በጣም አመቺና ተፈላጊ ናቸው፤ ቤተ ሙከራዎች ይፈልጓቸዋል!” ብያለሁ። ያው በዛሬዋ ኢትዮጵያ ላይ ምን እየተሠራ እንደሆነ የምናየው ነው፤ በሁሉም መስክ ሃገራችን ቤተ ሙከራ ሆናለች።

የሚገርም ነው፤ ይህ 'ጄፍሪ ኤፕሽታይን' የተሰኘው ዘንዶ 'ሞቷል' ከመባሉ በፊት የራሱን ዘረ መል በእያንዳንዱ የዓለም ነዋሪ አካል/ደም/መቅኒ ውስጥ የመቅበር ሕልም እንዳለው ተናግሮ ነበር። ኡ ኡ ኡ! የሚያሰኝ ነው፤ ነገር ግን እያንዳንዳችን 'ዊንዶውስ' የተሰኘውን የኮምፒተር ኦፕሬቲንግ ሲስተሙን ለዘመናት የምንገለገልለት ቢል ጌትስም ተመሳሳይ ህልም እንዳለው ማስረጃ የሚሆነን ለክትባት ያለው ልዩ ፍቅር ነው። ሉሲፈራውያኑ ብዙ ነው እያለሙ ያሉት። አዎ! አንዱና ዛሬ ያላቸው ዋናው መንገዳቸው ክትባት ነው። ምናልባትም በኮቪድ ክትባት በኩል ዘረ መላቸውን በመላው ዓለም አሰራጭተውት ሊሆን ይችላል። እነዚህን እርኩሶች የገሃንም እሳት ብቻ ነው የሚጠብቃቸው።

ግብረ-ሰዶማዊው የምዕብራውያኑ ዓለም በአፍሪቃውያን ላይ የሚፈጽመው በደል አልተገታም።


'ዎል ስትሪት ጆርናል' እንደዘገበው፤ 'ሞቷል' የተባለለትና የግራኝ አብዮት አሕመድ 'አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ' ሞግዚት የሆነው ሕፃናት ደፋሪው ጄፍሪ ኤፕሽታይን ከአንድ ሩሲያዊት ድልድይ ቁማር ተጫዋች ጋር ስለተፈጠረው ግንኙነት መረጃ በማቀበል የማይክሮሶፍቱን ቢል ጌትስን አስፈራርቶቷል።

☆ የጫካ ህግ

☆ አረመኔነት/ ሳዲዝም (በሰው ስቃይ፣ በሰው ችግር እና መከራ መደሰት ወይም ደግሞ የስቃይ ደስታን ለማግኘት ተብሎ ሰውን የማሳቃየት ድርጊት መፈጸም)☆ ሳይኮፓቲ (ናርሲስስቲክ ስብዕና እክል፣ የጠረፍ ስብዕና መታወክ እና ፀረ-ማህበረሰብ ስብዕና እክል ያለባቸው)

እነዚህ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች የአኗኗር ዘይቤዎች ናቸው።

የዓለማችን ቍ. ፩ ባለኃብትና አዲሱ የትዊተር ባለቤት፤ ኢለን ማስክ ለሰይጣናዊው የሃሎዊን-ኢሬቻ በዓል የባፎሜት-ፍዬል ያለበትን ሰይጣናዊ ልብስ ለብሶ ታይቷል።

ይህ አያስገርምም! የኢለን ማስክን የሕይወት ታሪክ ያነበበ፤ ይህ ትውልደ-ደቡብ አፍሪቃ የሆነ ግለሰብ ባጭር ጊዜ ውስጥ እንዴት ይህን ሁሉ ኃብት ሊያካብት ቻለ? ማን ፈቅዶለት? ብሎ እራሱን ለመጠየቅ ይደፍራል። ኢለን ማስክ ወንዳ-ገረድ' የተባለ ልጅ ሲኖረው፤ ደቡብ አፍሪቃዊው የእርሱ አባትም ከሚያሳድጋት ሴት ልጁ ሁለት ልጆች ወልዷል። ኢለን ማስክ አባቱን በጣም እንደሚጠላው ደጋግሞ ያወሳል። እነ ኢለን ማስክ + የፌስቡኩ ማርክ ዙከርበርግ + የአማዞኑ ጄፍ ቢዞስ + የጉግሉ ሰርጌ ብሪን + የአፕሉ ቲም ኩክ + የማይክሮሶፍቱ ቢል ጌትስ + ለጂኒው ግራኝ አብዮት አሕመድ የኖቤል ሰላም ሽልማት እንዲሰጠው ያደረገውና በእርሱም በኩል ኢትዮጵያውያንን ወደ አውሬነት ለመቀየር ያስችል ዘንድ (ጦርነቱ ወደ አዲስ አበባ እንዳይገባ የተፈለገበት አንዱ ምክኒያት፤ እንዳይፈርስ) ይሆን ዘንድ “የሳይንስ ማዕከል” (ሰው ሰራሽ የማሰብ ችሎታ / የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም)እንዲቋቋም ያደረገው ሴሰኛው ጀፍሪ ኤፕሽታይን ሁሉም ከጠፍር የመጡ ወይንም ከኒፌሊም ጋር ተዳቅለው የተገኙ የሳጥናኤል ፍጥረታት ሆነው ነው የሚታዩኝ። ሁሉ ነገራቸው በጣም አጠያያቂና አወዛጋቢ ነው!

Share on Google Plus

ስለ የተለጠፈበት ቀን

    Blogger Comment
    Facebook Comment