የፓሪሱ ኖትረ–ዳም ካቴድራል ከደረሰበት የእሳት ቃጠሎ ከተረፉትና ውድ ከሆኑት ጥቂት ቅርሶች መካከል ይህ የ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስጦታ የሆነው የኢትዮጵያ መስቀል አንዱ ነው።
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከ ስልሳ አምስት ዓመታት በፊት፡እ.ኤ.አ. በ 1954ዓ.ም፡ ወደ ፈረንሳይ በተጓዙ ጊዜ እግረመንገዳቸውን ሰሞኑን በእሳት የወደመውን የፓሪሱን “ኖትረ ዳም” ካቴድራል እና ቤተ–መቅደስ ጎብኝተው በዛውም ለፈረንሳይ አንድ ታላቅ የኢትዮጵያ መስቀል በስጦታ መልክ አበርክተው ነበር።
መስቀሉ የአለም መነጋገሪያ ሆኗል። ይህ ከቃጠሎው የተረፈው የኢትዮጵያ መስቀል አሁን ወደ ታዋቂው ሉቭር ቤተ መዘክር ተወስዷል።
ፈረንሳይ ይኼን ውድና ታላቅ መስቀል በኖትረ–ዳም ቤተ መዘክር አስቀምጣ ለ ስልሳ አምስት ዓመታት ያህልከጎብኚዎች ከፍተኛ ገቢ ታገኝበት ነበር።
ባለፈው ሳምንት ላይ የኖትረ–ዳም ካቴድራል ከነቤተ–መዘክሩ ሲቃጠል መስቀሉ ግን አንዳች ጉዳት ሳያደርስበት ተገኝቷል።
ወገኖቼ፤ ጊዜው እየተቃረበ ነው። የአለም አይኖች ሁሉ ድንቅ፣ ምስጢራዊ፣ የአለም እምብርት፣ የሕይወት ዛፍ እና የገነት መገኛ ወደሆነችው ኢትዮጵያ ይማትራሉ። አለም በአውሎ ነፋስ፣ በጎርፍ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በእሳት ስትናጥ ሁሉም መዳኛና መጠጊያ ወደሆነችው ወደ ኢትዮጵያ ፊቱን ያዞራል። አሁን ለጊዜው በአገራችን ሁሉም ነገር ደፍርሷል፤ ካልደፈረሰ አይጠራምና፡ ግን በቅርብ አገራችን ትጸዳለች፤ ጠላቶቿ ሁሉ አንድ ባንድ ይንበረከካሉ። የኢትዮጵያ ትንሳኤ ሩቅ አይደለም!
ነጠብጣቦቹን ስናገናኝ፦
ፕሬዚደንት ኢማኑኤል ማክሮን – ላሊበላ – ፓሪስ – ኖትረ–ዳም (የእኛ ወይዘሮ )– መስቀል – ስቅለት
በላሊበላ ካባ ለብሰው የነበሩት ማክሮንን እና አህመድ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ናቸው!
መስቀል ኀይላችን፣ ጽንዓችን፣ ቤዛችን፣ የነፍሳችን መዳኛ ነው!
Blogger Comment
Facebook Comment