ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ
እግዚአብሔር አምላካችን፤"በልጆቼ ላይ በደል የሚፈጽሙ ሰዎች፡ ዕምነት የሌላቸው ወይም እግዚአብሔርን ያልተቀበሉት ኃይሎች ለጥፋት ይላኩባቸዋል" ብሎ እንዳስተማረን፡ ኮሎኔል ጋዳፊ እና ከርሱ ጋር ለዘመናት አብረው ሲንደላቀቁ የቆዩት ሊቢያውያንም ለዚህ ክፉ ጊዜ በመድረስ፡ "ጨነቀኝ ጠበበኝ"ለማለት የበቁት፡ በተለይ፡ ኮሎኔሉ በክርስቲያኖች አምላክና በመንፈስ ቅዱስ ላይ ደግሞ ደጋግሞ ትዕቢት የተሞላባቸውን ስድቦች ለመሠንዘር በመቃጣቱ፡ እንዲሁም የሊቢያው ሕብረተሰብ፡ በተለይ በሀገረ ኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ ለዘመናት ሲፈጽመው ከነበረው ዲያብሎሳዊ አድራጎቱ የተነሳ ነው። የኢትዮጵያና እስራኤል ግኑኝነት እንዲሻክርና ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም እ.አ.አ. 1973 ዓ.ም ላይ ከእስራኤል እንዲርቁ ብሎም ወደ አረቦች እንዲጠጉና በመጨረሻም እንዲወድቁ ተደርገዋል። ይህም የሆነው ኢትዮጵያ በ አፍሪቃ አንድነት ድርጅት ዘንድ ፀረ–እስራኤል የሆነ አቋም እንድትይዝ የጋዳፊዋ ሊቢያ በርሷ ላይ ተጽእኖ ለማድረግ በመቻሏ ነበር። ልክ ከዚህ ጊዜ በኋላ ነበር ኢትዮጵያችን በጣም አስከፊ በሆነ መልክ እንድትራቆትና እንድትደቅ ሁለት የተዋሕዶ ትውልድም በተከታታይ እንዲጠፋ የተደረገው።
ሀገራችን ከእነዚህ ፍየል አገራት ጋር ማበር አልነበረባትም። ያልተባበሩት መንግሥታት በሊቢያ ስለሚካሄደው የባርነት ንግድና በእስላም ሀገሮች በበየቀኑ የሚታየው የክርስቲያኖች ጭፍጨፋ መውገዝ ነበረበት እንጂ ኢምባሲ ተዛወረ አልተዛወረ እንደ ትልቅ ነገር ተቆጥሮ የተለየ ሤራ መጠንሰስ አልነበረበትም። ትናንት በ ጎላን ከፍታዎች ጉዳይ እንዳየነው አሜሪካ ከእስራኤል ጋር ጥብቅብቅ ያለቸው ሎቢ የሚያደረጉ አይሁድ አሜሪካውያን ተጽዕኖ ማሳደር ስለሚችሉ ብቻ ሳይሆን፣ በዋናነት በረከቱን እንዳታጣ በመፍራቷ ነው።
በመታየት ላይ ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ብልሕነት የጎደለው አሠራር እና ተግባር የሚያስቆጣ ነው።
ዐቢይ ግራኝ አሕመድ የአረብ ሀገሮች መሪዎች በየሳምንቱ እየጋበዘ በመኪናው ሳይቀር ያንሸራሽራቸዋል፤ አገሮቻቸውንም በየወሩ ይጎበኝላቸዋል። ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ ተሰምቶ አይታወቀም። ሰውዬው ሀገራችንን ለመቅሰፍት እያዘጋጀልን እንደሆነ እንረዳው።
ልክ በ ካታሉኒያ (ስፔይን) + ቫሎኒያ (ቤልጂም) + ባቫሪያ (ጀርመን) + ክሮአስያ (ዩጎዝላቪያ) + ስኮትላንድ (ብሪታኒያ) + ቱርክ + ዩክሬየን (ሩሲያ) + ኩቤክ (ካናዳ) — እንደምናየው፡ ኦሮሚያ በተባለው ክልልም የአመጸኞቹ አለቃ ሰይጣን ከእርሱ መሰለፉን የመረጡትን ከሃዲዎች በተዋሕዶ ልጆች ላይ ያምጹ ዘንድ በመቀስቀስ ላይ ነው።
እግዚአብሔር የኢትዮጵያ ትንሣኤ ያሣየን!!!
Blogger Comment
Facebook Comment