ለህዝብ ድምጽ የሚሆኑ እንደ ቴዲ ያሉ ዕንቁ ልጆችን ጠብቁ!


✍ ቆሞስ አባ ጳውሊ | ከግንባር

አምባገነኑ የብልጽግና መንግስት ለምርጫ እየተዘጋጀ እንደሆነ ሁላችንም እናውቃለን። የአማራ ክልል ከትልልቅ የዞን ከተማ ውጭ ያሉ በርካታ የወረዳ ከተሞችና ሙሉ በሙሉ የገጠሩ ክፍል በፋ*ኖ የነፃነት ታጋይ ቁጥጥር ስር በመሆኑ መንግስት በጣም ጭንቅ ውስጥ ነው። በመሆኑም በከተማ ውስጥ ያሉ ሰዎች እያንዳንዳቸው ሶስትና ከዚያ በላይ የምርጫ ካርድ በግዴታ እንዲያወጡ ተደርጓል። አስባችሁታል አንድ ሰው ሶስት አራት ጊዜ ሊመርጥ! በቃ የህ*ጻን ጨዎታ መሆኑ ነው! መንግስት በአሁኑ ሰዓት ሀገሪቱ ችግር ውስጥ ባለችበት ሁኔታ ምርጫ ያሰበበት ዋነኛው ምክንያት ኢትዮጵያ ሰላም እንደሆነች ለማስመሰልና የህዝብን ስነ ልቦና ለመቀየር እንደሆነ ምንም የሚያጠራጥር ነገር አይደለም። በተጨማሪም ምርጫው ልክ እንደ ባህር በር አጀንዳ ነው! የሚለያዩት ባህር በሩ ቋሚ አጀንዳ ሲሆን ምርጫው ግን ለዚህ ዓመት ብቻ መሆኑ ነው! በመሰረቱ ትግራይና አማራ ያልተሳተፉበት ምርጫ ቀልድና ቧልት አይሆንም? አምባ*ገነኑ አብይ አህመድ በአሁኑ ሰዓት ይህን ምርጫ ለማድረግ በርካታ በጀት በጅቶ በገንዘብ በመደለልና በማስፈራራትም የምርጫ ድራማ እየሰራ ይገኛል። በተለይም ደግሞ ምርጫውን በጭ*ፍን ለሚከተሉት የብልጽግና አመራሮችና ደጋፊዎች ሀገራችን ፍጹም ሰላም ናት ለማለት ሊጠቀምበት አስቦ ስለመሆኑ ለሚያስተውል ሰው ይህ አይጠፋውም። 

ሆኖም ግን ሁላችንም እንደምናውቀው ብልጽግና የቀልድ የምርጫ ቅስቀሳ እያደረገ ባለበት ወቅት የኢትዮጵያ መከራ የገባው እውነተኛው የኢትዮጵያ ልጅ ዶክተር ቴወድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የምርጫ ድራማቸውን እንዳልሆነ አድርጎባቸዋል። ለዓለም ህዝቡ ሁሉ ኢትዮጵያ መከራ ውስጥ እንዳለች አጋልጧል። ይህም ለነፃነት የሚታገለው ፋ*ኖ የአማራ ህዝብ በማንነቱ ምክንያት በርካታ ግፍ እየደረሰበት በመሆኑ ይህን ግፍ ለመመከት ጫካ መግባቱን ስንነግራቸው የማይሰሙ ሰዎችን ዓይናቸውን እንዲገልጡ አድርጎልናል።  ኢትዮጵያ ችግር ውስጥ እንደሆነች ሁላችንም እያወቅን በጣም አንቀላፍተን ነበር። ግን ይህን ስል ሁላችሁንም ለማለት አይደለም። በርካታ የአማራ ተወላጆችና ሌሎችም የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰብ ህዝቦች ኢትዮጵያን ለማዳን በተዘዋዋሪ ፋ*ኖን በተለያየ መልኩ ሲያግዙ እያየን ነው። በርካቶች የኢትዮጵያውያን ፋ*ኖን ተስፋ አድርገው ተቀምጠዋል። እየመጡ ነው የሚለውም መፈክር ለዚህ ዋነኛ ማረጋገጫ ነው። ፋ*ኖ የአማራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ተስፋ ነው። ኢትዮጵያን የሚወድ ሁሉም ሰው ፍርሃትና ጥቅም ካልጋረደው በስተቀር ፋ*ኖን ተስፋ የማያደርግ ማንም የለም። የተበታተነችውና አንድነቷ፣መተሳሰቧ፣ፍቅሯ ፣ ሰላሟ ወዘተርፈ የሞቱባት ኢትዮጵያ የምትድነውና የምትነሳው ለፍትህና ለነፃነት በሚታገለው በአባቶቻችን የጀግንነት ወኔ ፣የአንድነትና የአብሮነት መንፈስ ባለው በኢትዮጵያ ፋና በፋ*ኖ ነው። 

በመሆኑም ግራ የተጋባው መንግስት በርካታ እቅዶችን እንዳቀደ መረጃ እየደረሰን ነው። ከዚህም መካከል የአዲስ አበባ ወጣቶችን ምርጫው ከመድረሱ በፊት እያፈሰሰ እስር ቤት ሊያስገባ ነው። ሰሞኑን በተለያየ ቦታዎች በማያስነቃ መልኩ በተናጠል በርካታ ወጣቶችን እያፈኑ ወደማይታወቅ ቦታ ወስደዋል። ስለዚህ ወጣቱ በየተራ እየተበላ ስለሆነ መፍትሄ መፈለግ ይኖርበታል። ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን፣ እውነታውን በመናገር ህዝብን የሚያበረቱ የሃይማኖት አባቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ የፊልም ባለሙያዎችን  ፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችን ወዘተርፈ እያሰረ፣እያፈነና እያስፈራራ ይገኛል። ሌላውና በጣም ሁሉም ሰው ማወቅ ያለበት ነገር አብይ አህመድ በዶክተር ቴዎድሮስ ካሳሁን ( ቴዲ አፍሮ) ላይ ብዙ አይነት የጥፋት እቅዶችን እያቀደ ነው። የመጀመሪያውን ሁላችንም እያየነው እንዳለው ማስጨነቅ ሲሆን የእርሱ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በማሰር ፣ወከባ በመፍጠርና ግራ በማጋባት በቤተሰብ እና በሱ ላይ ሽ*ብ*ር የመፍጠር ሲሆን ሌላውና ዋናው ደግሞ ተደጋጋሚ ፍተሻ በማድረግ በውሸት ቤቱ ውስጥ ህገ ወ*ጥ የጦ*ር መሳ*ሪያ ተገኘ በማለት ለማሰር ዝግጅት ላይ ናቸው።  ኢትዮጵያውያን ሆይ ይህን ዕንቁ አሳልፋችሁ እንዳትሰጡ! እንደ ዓይን ብሌናችን መጠበቅ አለብን! ከዚህ በዘለላም ሌላ የጥፋት መረብ ስለሚዘረጉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለዚህ ድንቅ ልጅ ደጀን መሆን አለባችሁ። እርሱ ኢትዮጵያ በችግሯ ሰዓት የቆመላት ብቸኛው ልጇ ነው። ስለዚህ ሁላችንም በማንኛውም መልኩ ከጎኑ ሆነን  የሚሆነውን ሁሉ በአጽንኦት መጠበቅ አለብን። 

በነገራችን ላይ ግን ምርጫው አብይ አህመድ ከአብይ አህመድ ጋር ነው እኮ! ብልጽግና መሩ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየቀለደ ነው! ምን አይነት ቀልድ ነው ግን? 

በድጋሜ የማሳስባችሁ ነገር ቢኖር ድምጽ ለሆናችሁ ሰው ደጀን ሁኑ! ቴዲን ጠብቁ! 

ድል ለኢትዮጲያ 


Share on Google Plus

ስለ የተለጠፈበት ቀን

    Blogger Comment
    Facebook Comment